top of page
Search

ዲያስፖራው አቶ ፋንታዬ አጋሮ ይባላሉ !!

  • Writer: kambattomai
    kambattomai
  • Jun 19, 2022
  • 1 min read

Updated: Apr 7, 2023

ለእናት ሀገሬና ወልዶ ላስተማረኝ ህዝቤ ባዶ እጄን አልሄድም ያሉት አንጋፋውና ምሁሩ የዲያስፖራ አባል አቶ #ፋንታዬ_አጋሮ ከሻንጣቸው ኪሎ ቀንሰው ያመጡትን የጤና መገልገያ ቁሳቁሶች ለዶዮገና ወረዳ አስተዳደር ታህሳስ 14/2014 አስረክበዋል ።

በአሜሪካ ሀገር ነዋሪ የሆኑት አንጋፋውና ምሁሩ አቶ ፋንታዬ አጋሮ (Tope Malla ፣ ) እና በሌሎችም ማህበራዊ ሚዲያ ጠቃሚ ሀሳቦችን ለሀገራቸውና ለተወለዱበት ማህበረሰብ በማስተዋወቅም ይታወቃሉ።

ካስረከቧቸዉ መሣሪያዎች፣ መድሃኒቶችና የተለያዩ የህክምና አገልግሎት የሚዉሉ ዕቃዎች መካካል ለአብነትም Pulse Oximeter (2), Infrared Thermometer (3), Touchless Therometer (2), Braun ThermoScan Thermometer (1), Braun Thero Scan Probe Covers 400 pcs, Face Masks (200), Digital Blood Pressure Monitor (1) Precision Neo FreeStyle Blood Glucos Monitoring System, Precion Neo FreeStyle Test Strips(50),Precion Neo Lancets (100), Binex COVID_19 Home Test Kit, Ear Wax Remval Aid (1), Toe Nail Nipper (1), Nail Clipper (1), Powder Free Vynyl Gloves (100pcs), Self Adhesive Bandages (3) እና ሌሎችም ይገኙበታል ።

ዲያስፖራው አቶ ፋንታዬ አጋሮ ወደ አሜሪካ ስመለሱ ላደረጉት መልካም አስተዋጽኦ ከወረዳው አስተዳደር የተዘጋጀውን የምስክርነት ወረቀት ተረክበዋል ስል የዘገበው የወረደው መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ነው ።

 
 
 

Recent Posts

See All
KAIF - KMG Ethiopia Partnership

ለዉድ ወገኖቻችንና ደጋፊዎቻችን በሙሉ ሰኔ 16 ቀን 2017 ዓ.ም. የከምባቶማ አክሽን ኢንተርናሽናል ፎረም (Kambattoma Action International Forum/KAIF) ከ KMG Ethiopia ጋር አብሮ...

 
 
 

Comments


Post: Blog2_Post
bottom of page